ናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር ለአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ከ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኦክሲጂን ሲሊንደርና ተያያዥ ግብአቶችን ድጋፍ አድርጓል ።
በድሬዳዋ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሽታ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ 35 ሺህ 499 ላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 5 ሺህ 231 የሚሆኑ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን የ 82 ሰዎች ህይወትም አልፏል ። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በድሬዳዋ አስተዳደር በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሽታ የሚያዙ እንዲሁም ህይወታቸው የሚያልፍ ዜጎች ከመጨመሩ ጋር ተያይዞ ለታማሚዎች የሚሆን የኦክስጅን እጥረትም እያጋጠመ ይገኛል ። ይህንንም ከግምት…


