ድሬዳዋን ጨምሮ የስድስት ከተሞች የመረጃ አስተዳደር በቅርቡ ስራ ይጀምራል::
የመረጃ አስተዳደሩ ከተሞች ራሳቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የሚሰሩትን ስራ ህዝብ እንዲያውቅላቸው፣ የሚሰጡት አገልግሎት እንዲተዋወቅ፣ ከውጭ የሚመጡ ሰዎች የተሟላ መረጃ እንዲያገኙ ለማድረግ የሚያስችል ነው ተብሏል። በዚህም አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ባህር ዳር፣ ሃዋሳ፣ አዳማ እና አርባምንጭ ከተሞች የከተማ መረጃ አስተዳደር እየለማላቸው ሲሆን÷ ራሳቸው ማስተዳደር እንዲችሉ ለባለሙያዎቻቸው በስራ አመራር ኢንስቲቲዩት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛልም ነው የተባለው። ስልጠናው ከተሞቹ የመረጃ አስተዳደሩን እንዲያስተዳድሩ፣…


