በ80 ሚሊየን ብር የተገነባው የድሬዳዋ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጫና ዘመናዊ መናኸሪያ ተመርቋል፡፡
መናኸሪያውን መርቀው ስራ ያስጀመሩት በፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ያደታ፥ መናኸሪያው ሁለተኛው ዙር የህዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት በተካሄደበት ማግስት መጠናቀቁ ለየት ያደርገዋል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በበኩላቸው፥ የመናኸሪያው መመረቅ ከዚህ በፊት በተጓዦች ይደርስ የነበረውን እንግልትና ዝርፊያ ያስቀራል ብለዋል። የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬዳዋ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰአዳ…


