በድሬዳዋ አሰተዳደር የቀበሌ 06 አስተዳደር ለጀግናዉ የመከላከያ ሠራዊታችን በአይነት ከ400 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረገ።

    የቀበሌ 06 ምክትል ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ቢፍቱ መሀመድ እንደገለጹት በቀበሌው አስተዳደር መከላከያ ሰራዊቱን በማጀገን ረገድ ባሉት አደረጃጀቶች ህብረተሰቡን በማሳተፍ ለጀግናዉ የመከላከያ ሠራዊት በርካታ ድጋፎች የተደረጉ ሲሆን ይህም ድጋፍ በአይነት ሩዝ ገብስ ፓስታ መኮረኒ ወ.ዘ.ተ ድጋፍ በማድረግ ህበረሰቡ ለጀግናዉ መከላከያ ሠራዊቱ ደጀንነቱን አሳይቷል፡፡
    በሴቶች አደረጃጀት እየተዘጋጀ ያለው ይህ የስንቅ ድጋፍ ለሰራዊቱ አለኝታነት ማሳያ እንደሆነም ነው ሀላፊዋ ያነሱት ።
    በስንቅ ዝግጅት ሲሳተፉ ያገኘናቸው የቀበሌው ነዋሪዎችም ሲገልጹ በወቅታዊ ሀገራችን ለህልውና ዘመቻ ከገንዘብ፣ከጉልበት ባሻገር የህይወት መስዋትነት ለመክፈል መዘጋጀታቸውንም በቁጭት በሞቀ የሀገራዊ ስሜት ተናግረዋል፡፡
    በሰላም ለማ
    ፎቶ፡- አብይ ሽመልስ