አዲስ ዓመት ሲመጣ፤ ወደ በርካታ ነዋሪዎች ጎጆ የሚገባውን፤ ለልጆች የመማሪያ ቁሳቁስ ማሟላት ያለመቻል ጭንቀት ለምታስወግዱ፤ ማንም ከትምህርት እንዳይቀር የአቅማችሁን በመደገፍ የምስኪን ወላጆችን እንባ ለምትጠርጉ፤ ለነገ አገር ተረካቢ ተማሪዎች ተስፋ ለሆናችሁ ቀሽቲ የድሬ ልጆች፣ ተቋማትና ግለሰቦች የከበረ ምስጋናዬን ሳቀርብ በኩራት ነው።

    በዘመናዊ ትምህርት እና በሥነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ለድሬዳዋችን ሁለንተናዊ ለውጥ ወሳኝ ነውና፤ ለአስተዳደራችን ተማሪዎች፣ መምህራን እና ለዘርፉ አካላት በሙሉ፤ 2015 አዲስ ዓመት በመልካም ውጤት የታጀበ ስኬታማ የትምህርት ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
    ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር