የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠናን ለማሳደግ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል – አቶ አህመድ ሽዴ
የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠናን ለማሳደግ፣ አገልግሎቱን ለማስፋፋት እና የታለመለት ግብ እንዲሳካ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ፡፡ በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የልዑካን ቡድን የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠናን ጎብኝቷል፡፡ የድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠናን ለማሳደግ፣ አገልግሎቱን ለማስፋፋት እና የታለመለትን ግብ ለማሳካት መንግስት ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ አህመድ ሽዴ አረጋግጠዋል። ነፃ የንግድ…


