የምወዳችሁና የማከብራችሁ ክርስቲያን ወገኖቼ፤ የገናን በዓል #እንዴት ለማክበር አሰባችሁ❓

ሁሌም በዓል ሲደርስ ከቤተሰብና ከወዳጅ ዘመድ ጋር በህብረት ማክበር የብዙዎቻችን ፍላጎትና ደስታ ነው። ልክ እንደ እኛ ይሄ ፍላጎት ኖሯቸው… በበዓል ቀን ህዝባቸውን ለማገልገል ሲሉ በፀጥታና ደህንነት፣ በህክምና፣ በትራንስፖርት፣ በሚዲያ እና ሌሎች ስራዎች ላይ የሚያሳልፉ ወገኖቻችን በርካታ ናቸው።
በአቅማችን የበዓል ስጦታ ይዘን፤ ብቻቸውን እንዳልሆኑ፣ ለአገልግሎታቸውም ልዩ ክብርና ምስጋና እንዳለን ብንገልፅላቸው፤ የሚያገኙት ደስታ ልዩ እንደሚሆን አምናለሁ። ለሰላምና ደህንነታችን ሲተጉ በፀረ ሰላም ሀይሎች ተጎድተው፤ በፌዴራል ፖሊስ ሆስፒታል የሚታከሙ ወንድምና እህቶቻችን በጎበኘንበት ወቅት፤ ከፊታቸው ላይ ያየነው ይሄን ስሜት ነበር።