በሁለም የገጠር ቀበሌዎች ለ18 ቀናት ሲከናወን የቆየው የ2016 ዓ.ም የተቀናጀ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ስራዎች ማጠቃልያ ሪፖርት በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በተገኙበት ቀርቦ ተገምግሟል።
በማጠቃለያ መድረኩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በተፋሰስ ልማት ስራው ላይ የተሳተፉ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ላከናወኑት ስራ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆ፤ በዚህ በዘንድሮ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ስራ የአርሶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት የሚቀይሩ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።
በተለይም በጤና መድህን ላይ በሁሉም ቀበሌ ጥሩ አፈፃፀም መመዝገቡን የገለፁት ደግሞ የድሬደዋ አስተዳደር ውሃ ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ ኑረዲን አብደላ ናቸው።
በነገው ዕለት የማጠቃለያ የእውቅናና የሽልማት ፕሮግራም እንደሚኖር ከወዲሁ ታውቋል።


