”ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ቃል በድሬዳዋ አስተዳደር ውይይት ተደረገ

በ2ኛው የብልጽግና መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች በወረዳዋች ለብልጽግና ህብረት አባላት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

በመድረኩም የኢኮኖሚ ልማትን ማፋጠን፣ ማህበራዊ ብልጽግናን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ውጤታማነት ማስቀጠል፤ውጤታማ የዲፕሎማሲ ስራ መስራት፤የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ውጤታማነትን ማረጋገጥ፤ጠንካራ የሚዲያ እና የኮሙዩኒኬሽን ስራ መስራት፤የጠንካራ ፓርቲ ግንባታን አጠናክሮ መቀጠል፤የብሔራዊነት ገዢ ትርክት ግንባታ ማጠናከር፤ውጤታማ የሰላም ግንባታ መስራት፤የፍትህ ዘርፍ ውጤታማነትን ማሳደግ፤የሀገር ግንባታ ማጠናከር፤ ነጥቦችን የያዘ ሰነድ ቀርቧል።

በወረዳ 6,7,8,9 በተካሄደው የውይይት መድረኩ ለአባላቱ በፓርቲው ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎች እና የተቀመጡ አቅጣጫዎችን የያዘ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *