ድሬዳዋን በቴክኖሎጂ ማበልፀግና ማዘመን እንደሚገባ ተገለፀ

የድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ለከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ለሶስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል ።

በዛሬው እለት በነበረው የስልጠና መርሀ-ግብርም ስማርት ሲቲን መገንባት ብሎም ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት በቴክኖሎጂ ማበልፀግ እንደሚገባና በተለይም የአስተዳደሩ መሬት ልማት ፣ ገቢዎች ባለስልጣን እንዲሁም ፖሊስ ኮሚሽን አሰራራቸውን በቴክኖሎጂ ማበልፀግ መቻላቸው ለተገልጋዩም ማህበረሰብ ቀልጣፋ የሆነ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉም በእጅጉ እንደሚረዳም ነው የተገለፀው ።

ሌሎች ተቋማትም አገልግሎታቸውን በቴክኖሎጂ የታገዘ ከማድረግ ጋር ተያይዞ ጅምር ስራዎች እየተሰሩ እንዳሉና ነገር ግን የተጀመሩት ስራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው አገልግሎታቸውን በቴክኖሎጂ በመታገዝ መስራት እንደሚገባቸውም ነው የተገለፀው ።

በአለማየሁ አበበ

ፎቶ:-አገኘሁ ሸዋረጋ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *