በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ ጅማ ከተማ ገቡ።

ወደ ከተማዋ ሲደርሱ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮችን ጨምሮ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከነገ ጀምሮ ለ2 ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የሌማት ትሩፋት ምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኢትዮጵያ አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም መድረክ ላይ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል ያካሄድናቸው ጥረቶች እና የተገኙ ልምዶች በስፋት ይገመገማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *