በድሬዳዋ አስተዳደር ሲካሄድ የነበረው የትምህርት ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር ተጠናቀቀ

ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም መርህን ከግብ ለማድረስ በስፖርት የበለፀገ ዜጋን ማፍራት ወሳኝ ነው በሚል መሪ ሀሳብ የ 2017 ዓ.ም የመንግስት እና የግል አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመታዊ የተማሪዎች ስፖርት ውድድር በዛሬው እለት ተጠናቋል ።

ስፖርታዊ ውድድሩም ባለፍት ሁለት ወራት ሲካሄድ የነበረ ሲሆን በዚህም ስፖርታዊ ውድድር ላይም 42 የከተማ ትምህርት ቤቶች በ 8 የስፖርት አይነቶች ከ 4500 በላይ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል ። አዲሱ ትምህርት ቤት ከለገሀሬ ትምህርት ቤት ባደረጉት የእግር ኳስ ጨዋታ ውድድሩም ፍፃሜውን አግኝቷል ።

አዲሱ ትምህርት ቤት ከ ለገሀሬ ትምህርት ቤት ባደረጉት የፍፃሜ እግር ኳስ ጨዋታም አዲሱ ትምህርት ቤት 4 ለ 2 በሆነ ውጤት ለገሀሬ ትምህርት ቤትን ማሸነፍ ችሏል ። በ 8 የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ላይ ውጤታማ ለሆኑ ትምህርት ቤቶች እና ተማሪዎች እንዲሁም ለውድድሩ መሳካት አስተዋፆ ላበረከቱ አካላት የተለያዩ ሽልማቶችም ተበርክቶላቸዋል ።

በአለማየሁ አበበ

ፎቶ :- በአገኘው ሸዋረጋ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *