በድሬዳዋ አስተዳደር በማህበረሰቡ እና በአመራሩ ቅንጅታዊ አሰራር መዳበር ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸው ተገለፀ

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የተመራ ልዑካን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል። ልዑኩ ከድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ከክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን እንዲሁም ከድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ከክብርት ወ/ሮ ከሪማ አሊ ጋር በጋራ በመሆን የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠናን፣ ደረቅ ወደብን፣ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የአዲስ…

Read More

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት በክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የተመራ ልዑካን ቡድን ሀገር አቀፍ የሕግ ተርጓሚዎች መድረክ ላይ ለመሳተፍ ድሬዳዋ ከተማ ገባ

ልዑክ ቡድኑ ድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ፣ በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን፣ በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ በክብርት ወ/ሮ ከሪማ አሊ እንዲሁም በአስተዳደሩ በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።ልዑክ ቡድኑ በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን እንደሚጎበኝም ከወዲሁ ተጠቁሟል።

Read More

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የእውቅና ሽልማት በትላንትናው እለት አበረከተች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በ44 ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ለድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የእውቅና ሽልማት አበረከተች። ሽልማቱን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ለከንቲባው ተወካይ እና የድሬዳዋ አስተዳደር የከንቲባ ጽ/ቤት እና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ለአቶ ገበየሁ ጥላሁን አስረክበዋል። ከንቲባ ከድር ጁሀር የኢትዮጵያ…

Read More