የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3 ተኛ የስራ ዘመን 5 ተኛ ዓመት 11 ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል::

በጉባኤውም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የምክር ቤቱ 3 ተኛ የስራ ዘመን 5 ተኛ ዓመት 11 ኛ መደበኛ ጉባኤ አጀንዳ እና የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የምክር ቤቱን 3 ተኛ የስራ ዘመን 5 ተኛ ዓመት 3 ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ፀድቋል ።

በጉባኤውም የአስተዳደሩ የአስፈፃሚና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የ 2018 ዓ.ም የ 6 ወር የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት በድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር የቀረበ ሲሆን ሪፖርቱንም መነሻ በማድረግ የቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም የምክር ቤት አባላት የተለያዩ ሀሳብ አስተያየቶችን አንስተዋል ።

ከጤና ጋር ተያይዞ ከብሄራዊ ደም ባንክ በተገኘ የዲጂታል የደም ምርመራ ማሽን ፣ በብልሽት ይወገድ የነበረ ደም መጠን መቀነስ ፣ ከዚህ ቀደም የደም ማጣራት ረጅም ጊዜ ይወስድ የነበረው ያጠረበት ፣ በአንድ ጊዜም ቡዙ የደም ሳምፕል ማጣራት መቻሉ አበረታች መሆኑን አስታውቀዋል ። በትምህርቱ መስክም በከተማ እና በገጠር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በቀጣይ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስታውቀዋል ።

ከመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ጋር ተያይዞ ሳምንታዊ ሬዲዮ እና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞች ፣ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ስፖቶች ፣ ዶክመንተሪ ፊልሞችን በማዘጋጀት እንዲተላለፍ ከማድረግ አኳያ እንዲሁም ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይም የተለያዩ መረጃዎች እና ዜናዎች እንዲሰራጭ መደረጉ አበረታች መሆኑ በጉባኤው ላይ ተነስቷል።

በአስተዳደሩ ገቢን የመሰብሰብ አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የአስተዳደሩን ወጪ በገቢ ለመሸፈን በአስተዳደሩ የተለያዩ የገቢ ምንጮችን በሚገባ በመለየት የገቢ አቅምን ከማሳደግ ረገድ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አስታውቀው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የአስተዳደሩን ነዋሪዎች እና የፀጥታ ሀይሎች በቅንጅት ተባብረው በመስራታቸው የተመዘገበው መልካም ውጤት እጅግ አበረታች ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ነው ያስታወቁት ።

መደበኛ ጉባኤው ከሰአትም የሚቀጥል ይሆናል ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *