‹‹ቤቶችን ለመንግስት ያለማስተላለፍ ችግር አሠራራችን ላይ ማነቆ ፈጥሯል››
የመረጃ አያያዝ ክፍተትም ለህገ-ወጥነት በር ከፍቷል፡፡ አቶ እውነቱ ወርቅነህ የድሬዳዋ አስተዳደር ቤቶች ኮርፖሬሽን ስራ አስኪያጅ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የሆነው የድሬዳዋ አስተዳደር ቤቶች ኮርፖሬሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈጻፀሙን ለጋዜጠኞች በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡፡ በአፈፃፀሙም በርካታ ያልተከፈሉ ውዝፍ እዳዎችን የማስከፈል፣ በህገ ወጥነት የተያዙ ቤቶችን የማስመለስ፣ ከእገዳ በፊት የኮርፖሬሽኑን መመሪያ ለደንበኞች ቀድሞ የማስተዋወቅ፣ ቅርንጫፍ…


