በዚህ ቅስቀሳ ስነስርዓት ላይ የብልፅግና ፓርቲ አባል የመንግስት ሰራተኞች የድጋፍ እና የቅስቀሳ ስነስርአት በከተማዋ የተለያዩ አቅጣጫዎች አካሄደዋል፡፡
በቅስቀሳው ላይ የድሬደዋ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መብራቴ ገብረየስ ፓርቲው በድሬ ደዋ እድገት ላይ እንቅፋት የሆነውን ቻርተር ማሻሻል፣ በከተማው ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ የአፋን ኦሮሞ እና ሶማሊኛ ቋንቋ የስራ ቋንቋ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል ፡፡


