በድሬዳዋ አስተዳደር ፀረ-ሰላም ሀይሎች ገብተዋል ተብሎ የሚናፈሱ ወሬዎች ፍፁም ከእውነት የራቁ መሆናቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ።
ፖሊስ ኮሚሽኑ ከምን ጊዜውም በላይ የከተማዋን ሰላም ለማስጠበቅ በመስራት ላይ እንደሚገኝም ተገልፆል ። የድሬዳዋ አስተዳደር የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችና እምነት ተከታዮች በጋራ በአንድነት ተቻችለውና ተከባብረው እንደሚኖሩባት ይታወቃል ነገር ግን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የከተማዋን በጋራ የመኖር እሴትን ለማደፍረስ የሚጥሩ ፀረ-ሰላም ሀይሎች ወደ ከተማዋ እንደገቡ ተደርጎ ያልተጨበጡና ፍፁም ከእውነት የራቁ መረጃዎችን ህብረተሰቡ ዘንድ እየተሰራጩ ይገኛሉ ። እነዚህም መረጃዎቹ…


