በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በህግ ማስከበር ተሳትፎ ጉዳት ደርሶባቸው በምስራቅ እዝ ደረጃ ሶስት ሆስፒታል በህክምና ላይ የሚገኙ የሰራዊት አባላትን ለማበረታታት ያለመ ፕሮግራም ተካሄደ ።

    የኢ.ፌ.ድ.ሪ መከላከያ ሰራዊት ከሀገር ውስጥ ብሎም ከሀገር ውጪ የሚቃጣበትን ጥቃት ከመመከት ባለፈ ቀን ከለሊት የሀገሩን ዳር ድንበር በማስከበር ላይ ይገኛል ። ይህንንም ተከትሎ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው የህግ ማስከበር ተልእኮ ላይ ተሳትፈው ጉዳት ደርሶባቸው በምስራቅ እዝ ደረጃ ሶስት ሆስፒታል በህክምና ላይ የሚገኙ የሰራዊት አባላትን ማበረታታትና ከጉዳታቸውም አገግመው ወደ ግዳጅ እንዲቀላቀሉ ለማበረታታት ይቻል ዘንድ እንዲሁም የፌደራል…

    Read More

      በመላ ድሬዳዋ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ ዛሬ ዕለተ ስቅለት በድምቀት ተከበረ::

      በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ የካቲት መጨረሻ ላይ የተያዘው የአብይ ጾም በጾምና በጸሎት አምላክን በመለመንና በመማጸን አሳልፈው ጾሙ ሊገባደድ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል፡፡ በተለይም በአብይ ጾም የመጨረሻው አርብ ከሌላው ቀናት ለየት የሚያደርገው ኢየሱስ ክርስቶች በመስቀል ላይ እሱ ሞቶ ለመላ የሰው ልጆች ህይወት የሰጠበት ዕለት በመሆኑ ቀኑን በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ይከበራል፡፡ ስለሆነም ይህን በማሰብ በመላ…

      Read More

        የድሬዳዋ አስተዳደርን ጨምሮ የምስራቅ ሀረርጌ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሶስት ቀናት ከፍተኛ የሆነ ዝናብ ሊጥል እንደሚችል ተገለፀ ።

        ነዋሪው ህብረተሰብም ተገቢውን ቅድመ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባም ተገልፃል ። የድሬዳዋ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት በከተማችን ድሬዳዋ ብሎም በአጎራባች ክልሎች አደጋ ከመድረሳቸው አስቀድሞ በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች ለአደጋው ቅድመ መረጃ ኖሯቸው ለአደጋው ተጋላጭ እንዳይሆኑ ብሎም ሊደርስ ከሚችል ጉዳት እራሳቸውን እንዲከላከሉ ተገቢውን መረጃ ይሰጣል ። ከዚህም ባለፈም ይህንን ስራ ለሚሰሩ አስፈፃሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶች…

        Read More

          በቀበሌ 06 አስተዳደር 200 ለሚሆኑ ችግረኛ ነዋሪዎች ድጋፍ ተደረገ::

          የቀበሌ 06 አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም በአካባቢው ላይ ለከተማ ምክር ቤት የብልጽግና ፓርቲን ወክለው የሚወዳደሩ እጩዎች በቀበሌው ከሚገኙ ባለሀብቶችና የንግድ ማህበረሰቦች ባሰባሰቡት ገንዘብ 200 ለሚሆኑ ለአካባቢው ችግረኞች የታለቁን ረመዳን ጾምና የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ ተደርጓል፡፡ በድጋፍ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ም/ከንቲባና የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ከድር ጁሀርን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የብልጽግና…

          Read More

            በድሬዳዋ አስተዳደር ፀረ-ሰላም ሀይሎች ገብተዋል ተብሎ የሚናፈሱ ወሬዎች ፍፁም ከእውነት የራቁ መሆናቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ።

            ፖሊስ ኮሚሽኑ ከምን ጊዜውም በላይ የከተማዋን ሰላም ለማስጠበቅ በመስራት ላይ እንደሚገኝም ተገልፆል ። የድሬዳዋ አስተዳደር የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችና እምነት ተከታዮች በጋራ በአንድነት ተቻችለውና ተከባብረው እንደሚኖሩባት ይታወቃል ነገር ግን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የከተማዋን በጋራ የመኖር እሴትን ለማደፍረስ የሚጥሩ ፀረ-ሰላም ሀይሎች ወደ ከተማዋ እንደገቡ ተደርጎ ያልተጨበጡና ፍፁም ከእውነት የራቁ መረጃዎችን ህብረተሰቡ ዘንድ እየተሰራጩ ይገኛሉ ። እነዚህም መረጃዎቹ…

            Read More

              በሁሉም ከተማ ቀበሌዎች ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በአስተዳደሩ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡

              ከ2014-2016ዓ.ም የድሬዳዋ ከተማ የካፒታል ኢንቨስትመንት ዕቅድ (CIP)ዝግጅት አስመልክቶ የከተማው ህብረተሰብ እና የባለድርሻ አካላት ጋር በእቅድ ዝግጅቱ እንዲካተቱ የሚያስፈልጉና አዲስ ኘሮጀክቶች ላይ ውይይት እየተደረገ ይገኛል፡ ፡ በአስተዳደሩ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች ከፕሮጀክቶቹ መካከል ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥረው የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ ስራን ጨምሮ የጠጠር መንገድ፣ የጎርፍ መከላከያ ግንብ፣ አዲሱ ቄራ፣ የመንገድ መብራት፣ ፓርክና የመንገድ አካፋይ ግንባታና አረንጓዴ…

              Read More

                የተፈጠረውን የኦክስጂን እጥረት ለማቃለል ባለሀብቶች ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል ተባለ፡፡

                በድሬዳዋ ጤና ቢሮ የኮቪድ-19 ህክምና ማዕከል ለሆነው የፈረንሳይ ሆስፒታል ክሮምቶ ማኑፋክቸሪንግ ፒልሲ 50 ኦክስጂን የተሞላባቸውን ሲሊንደሮች በድጋፍ አበርክቷል፡፡ በድጋፍ አሰጣጡ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ዕለት ተዕለት የኮቪድ-19 ስርጭት መጠን መስፋፋቱን ተከትሎ በአስተዳደራችን የህሙማን ቁጥርም በመጨመሩ ምክኒያት የተከሰተውን የኦክስጂን እጥረት ግምት ውስጥ በማስገባት ክሮምቶ ማኑፋክቸሪንግ ፒልሲ ላደረገው የኦክሲጂን ሲሊንደሮች ድጋፍ ምስጋናቸውን…

                Read More

                  ስፖርታዊ ውድድሮች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውን በማሻሻል የሀገር ልማት ላይ ከፍተኛ ፋይዳ እንዲኖረው ከማድረግ በዘለለ ለወጣቶችም የስራ እድል እንዲፈጥር መሰራት እንዳለበት ተገለፀ፡፡

                  በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ ለሚገኘው የቤትኪንግ ኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር መሳካት የጎላ ሚና ለነበራቸው አካላት የእውቅና ፕሮግራም ተዘጋጅቷል፡፡ የ 2013 የቤትኪንግ የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ ይገኛል፡፡ 4 ተኛው ዙር የቤትኪንግ የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ 13 ክለቦች ተሳታፊ ሆነው ውድድራቸውን እያካሄዱ ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞም ውድድሩ በተሳካ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱ የሚዲያ…

                  Read More

                    የድሬዳዋ ልጆች እና ወዳጆች አለም አቀፍ ማህበር” ለአቅመ ደካማ ነዋሪዎች ድጋፍ አደረገ::

                    በአስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን ሁለገብ ሜዳ በተካሄደው የድጋፍ መርሀግብር ላይ ወ/ሮ ሜላት ብርሀኔ ማህበሩን በመወከል ባደረጉት ንግግር በአሜሪካና በአውሮፓ በሚኖሩ የድሬዳዋ ተወላጆች የተመሰረተው ማህበር በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ሰብአዊ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል:: በዛሬው ድጋፍም ከተለያዩ የአስተዳደሩ የከተማ ቀበሌዎች ለተመረጡ 200 አቅመ ደካማ የእስልምና እና ክርስትና እምነት ተከታዮች በዓል መዋያ የሚሆን ለእያንዳንዳቸው 1ሺህ ብር…

                    Read More

                      ሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መሳሪያ በሀገር ውስጥ አቅም በማምረት ለኮቪድ 19 ፅኑ ህሙማን ለማድረስ እያደረገ ያለው ጥረት እየተሰናከለ መሆኑን ሬዳዋ ሞተርስ ኢንዱሰትሪ ኃ/የተ/የግ ማህበር አስታወቀ፡፡

                      መቀመጫውን ድሬዳዋ ያደረገው ሬዳዋ ሞተርስ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የኢንጅነሪንግ ክፍል ማናጀር ኢንጅነር ምንያህል ደበበ እንደተናገሩት ድርጅቱ በአሁን ሰአት የበርካቶችን ህይወት እየቀጠፈ የሚገኘውን የኮቪድ 19 ወረርሽን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ፡፡ ድርጅቱ ወርሽኙ ከተከሰተ ወዲህ ከፍተኛ እጥረት የሚታይበትን ሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መሳሪያ (መካኒካል ቬንትለት) በሀገር ወስጥ በራስ አቅም ለማምረት ሰፊ ግዜና በጀት…

                      Read More