አራቱ የገጠር ፖሊስ ጣቢያዎች በድጋፍ የተበረከተላቸውን ዘይት ፤ፓስታ እና ሩዝ ተረከቡ ፡፡
በዛሬው እለት በአራቱም ገጠር ፖሊስ ጣቢያዎች ተገኝተው የምግብ ሸቀጣሸቀጦቹን ያስረከቡት የድሬዳዋ አስተዳዳር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ እና የሰው ሀብት ልማት ዘርፍ ሃላፊ ም/ኮሚሽነር ውቢት በፍቃዱ ናቸው፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ የምግብ ሸቀጦቹን ለፖሊስ አባላቱ ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት ፖሊስ የህዝቡን ሰላም እና ደህንነት ማረጋገጥ ከቻለ የህዝብን አመኔታ መፍጠር ይችላል ብለዋል፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር…


