በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በህግ ማስከበር ተሳትፎ ጉዳት ደርሶባቸው በምስራቅ እዝ ደረጃ ሶስት ሆስፒታል በህክምና ላይ የሚገኙ የሰራዊት አባላትን ለማበረታታት ያለመ ፕሮግራም ተካሄደ ።
የኢ.ፌ.ድ.ሪ መከላከያ ሰራዊት ከሀገር ውስጥ ብሎም ከሀገር ውጪ የሚቃጣበትን ጥቃት ከመመከት ባለፈ ቀን ከለሊት የሀገሩን ዳር ድንበር በማስከበር ላይ ይገኛል ። ይህንንም ተከትሎ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው የህግ ማስከበር ተልእኮ ላይ ተሳትፈው ጉዳት ደርሶባቸው በምስራቅ እዝ ደረጃ ሶስት ሆስፒታል በህክምና ላይ የሚገኙ የሰራዊት አባላትን ማበረታታትና ከጉዳታቸውም አገግመው ወደ ግዳጅ እንዲቀላቀሉ ለማበረታታት ይቻል ዘንድ እንዲሁም የፌደራል…


