ምስራቃዊ የእድገት ፋና የበጎ አድራጎት ማህበር 6 ተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ለመታዘብ ለተመረጡ ታዛቢዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል ።
በ 2001 ዓ.ም የተመሰረተው ምስራቃዊ የእድገት ፋና የበጎ አድራጎት ማህበር በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ በከተማም ሆነ በገጠር ጤና ላይ ፣ ትምህርት ፣ ኤች.አይ.ቪ እንዲሁም የተለያዩ ማህበራዊ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል። ምስራቃዊ የእድገት ፋና የበጎ አድራጎት ማህበር እያከናወናቸው ካላቸው ዘርፈ-ብዙ የማህበራዊ አገልግሎት ስራዎች በዘለለ የፊታችን ሰኞ የሚካሄደውን 6 ተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ተከትሎ ምርጫው ሰላማዊና ፍትሀዊ በሆነ አግባብ…


