ሁሉም ዜጋ ለሃገር ልማት በተሰማራበት ዘርፍ የዜግነት ግዳታውን መወጣት እንደሚገባ የድሬደዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ሰራተኞችና ግብር ከፋዮች ገለፁ ::

    የባለስልጣኑ ሰራተኞችና ግብር ከፋዮች የችግኝ መትከል እና የደም ልገሳ ስነስረአት አካሂደዋል። በስነስረአቱ ላይ የድሬደዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱሰላም መሃመድ ባለስልጣኑ ለሃገር ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ የሆነውን ግብር ከመሰብሰብ ተልእኮውን ከመወጣት ጎንለጎን ስራተኞቹና ደንበኞቹ በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባር እንዲሳተፉ እንደሚሰራ ተናግረዋል። አክለውም አሁን ላይ እንደሃገር እየተከናወነ ያለውን የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ የበኩላቸውን ለመወጣት እንደዚሁም የአገርን…

    Read More

      ለሀገራዊ ጥሪ ምላሽ ለመስጠት የሚንቀሳቀሰውን የድሬዳዋ አስተዳደር ልዩ ሃይል አባላት ሽኝት ተደረገላቸው ።

      የአሸባሪውን የህውሀት ጁንታ ቡድን ሀገርን የማፈራረስና የመበታተን የሽብር ተግባርና ተልእኮ የማምከንና ህግን የማስከበር ሀገራዊ ጥሪን ተከትሎ በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ልዩ ሀይሎች ሀገራዊ ጥሪውን ተቀብለዋል ። ይህንንም ሀገራዊ ጥሪ በመቀበልም በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ የልዩ ሀይሎች በሀገራዊው የህግ የማስከበር ዘመቻ ለሚሳተፉ የአስተዳደሩ ፖሊስ ኮሚሽን የልዩ ሀይል አባላት የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባና የካቢኔ አባላቶቻቸው፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶችና…

      Read More