የሀዘን መግለጫ የድሬደዋ ባለውለታ የሆኑት መምህር ስለሺ ካሳዬ ወ/ሚካኤል ባደረባቸው ህመም ምክንያት ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።

    መምህር ስለሺ ካሳዬ ከአባታቸው ካሳዬ ወ/ሚካኤል እና ከእናታቸው ወ/ሮ ፈለቀች ደበበ ህዳር 12/1931 ዓ.ም በጉርጉሱም አውራጃ ፈናን ቢራ ከተማ ተወለዱ ።
    መምህር ስለሺ ባለትዳርና የአራት ወንድ ልጆችና የሁለት ሴት ልጆች አባት ነበሩ ።
    በ2010 በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው በበጎ ሰው ሽልማት በመምህርነት ዘርፍ ተሸላሚ መሆን ችለዋል ።
    የድሬደዋ አስተደደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ሰራተኞች እና አመራር የተሰማንን ልባዊ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን ።