የሀዘን መግለጫ የድሬደዋ ባለውለታ የሆኑት መምህር ስለሺ ካሳዬ ወ/ሚካኤል ባደረባቸው ህመም ምክንያት ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።
መምህር ስለሺ ካሳዬ ከአባታቸው ካሳዬ ወ/ሚካኤል እና ከእናታቸው ወ/ሮ ፈለቀች ደበበ ህዳር 12/1931 ዓ.ም በጉርጉሱም አውራጃ ፈናን ቢራ ከተማ ተወለዱ ። መምህር ስለሺ ባለትዳርና የአራት ወንድ ልጆችና የሁለት ሴት ልጆች አባት ነበሩ ። በ2010 በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው በበጎ ሰው ሽልማት በመምህርነት ዘርፍ ተሸላሚ መሆን ችለዋል ። የድሬደዋ አስተደደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ሰራተኞች እና አመራር የተሰማንን…


