የሀገር መከላከያ ሰራዊታችንን በየትኛውም መልኩ በመደገፍ ለሀገር ሉአላዊነት መከበር የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ በትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬደዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የስራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች አስታወቁ፡፡
የተቋሙ ሰራተኞች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የበአል መዋያ ሚውሉ ሁለት ሰንጋዎች እና የገንዘብ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ በስነስረአቱ ላይ በመገኘት ስጦታውን ያበረከቱት በፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬደዋ ቅርንጨፍ ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰአዳ አዋሌ እንደተናገሩት እስከህይወት መስዋትነት እየከፈሉ ሀገርን ለማስቀጠል ሚዋደቁ የሀገር ባለውለታዎቻችን በመሆናችሁ በአልን አብረን ነን ለማለት የእለቱን ድጋፍ አድርገናል ብለዋል፡፡ በቀጣይም ሚደረገውን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው ዋና…


