የውጭ ሀገራትን አኮኖሚያዊ ተጽዕኖ ለመቀልበስ እንደተቋማችን በተሰማራንበት የሙያ መስክ ጠንክረን በፍፁም የአገልጋይነት መንፈስ ለሀገር እድገት እንሰራለን አሉ በትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬደዋ ቅርንጫፍ ዋና ዳሬክተር ወ/ሮ ሰአዳ አዋሌ፡፡ የተቋሙ የማኑጅመንት አባላት እና ሰራተኞች የ”ነጩ ፖስታ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት” ንቅናቄን አካሂደዋል።
በስነ-ስረአቱ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬደዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዋና ዳሬክተር ወ/ሮ ሰአዳ አዋሌ እንደተናገሩት ሀገራችን በዓለም አደባባይ ያላትን ገጽታ ለማበለሻት በተጠና መልኩ እየተንቀሳሰቀሱ ያሉ ሃይሎችን መረጃ ሃሰት መሆኑን ለማሳወቅ ሁላችንም የሀገር ገጽታን እና ያለውን እውነታ በመሰል የንቅናቄ መርሀግብሮች እና የማህበራዊ ገፆችን በመጠቀም ለውጭ አለማት ማስገንዘብ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ ሌላው ደግሞ አሉ ወ/ሮ ሰአዳ…


