በትውልዶች ታሪክ የማይረሳ አስነዋሪ ድርጊት የፈፀመው አሸባሪው የህወሓት አረመኔ ቡድን፤ በኢትዮጵያውያን ብርቱ ክንድ ግብዓተ መሬቱ እየተፈፀመ በሚገኝበትና፤ መላው ኢትዮጵያዊያን በችግር ጊዜ በአንድነት የምንቆም ጽኑ ህዝቦች መሆናችንን፤ ለአለም በተግባር እያሳየን በምንገኝበት በዚህ ወቅት በዓሉ መከበሩ ደግሞ እጅግ ልዩ ያደርገዋል።
የፀጥታ አካላት፤ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ግለሰቦች፤ እንዲሁም የንግዱ ማህበረሰብ፤ በአጠቃላይ መላው የድሬዳዋ ነዋሪዎች ለበዓሉ ስኬት የድርሻችሁን ጠጠር በመጣል ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ጥሪ እያቀረብኩ፤ በአስተዳደራችን ከዚህ ቀደም በሌብነት ሂደት ተከናውነው ህጋዊ የመሠሉ፤ በርካታ ህገ-ወጥ ድርጊቶችና ብልሹ አሰራሮችን በማፅዳት፤ የጀመርነውን አስተዳደራዊ የልማትና የዴሞክራሲ ጉዞ፤ ከበዓሉ ማግስት ጀምሮ አጠናክረን እንደምንቀጥል አረጋግጥላችኋለው።
ክቡር አቶ ከድር ጁሀር
የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ


