ጎህ ቤቶች ባንክ አክስዮን ማህበር በቅርቡ 1.056 ቢሊዮን ብር ካፒታል ከብሔራዊ ባንክ ባገኘው ፍቃድ መሰረት በአዲስ አበባ የመጀመሪያ ባንኩን በወረሀ ጥቅምት 2014ዓ.ም መመስረቱ ይታወሳል በዛሬው እለትም በድሬዳዋ የመጀመሪያ ቅርንጫፍ ባንክ በሳቢያን ብሪጅ ካፌ ህንጻ ላይ የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህና ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በይፉ ተከፍቷል።
በምርቃ ስነ-ስርአቱ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አሰተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ እንደተናገሩት የመኖሪያ ቤት እጥረት ካሉብን ችግሮች መካከል አንዱና ዋንኛ በመሆኑ ይህ ችግር ከአስተዳደሩ ጎን በመሆን እገዛ እንደሚያደርግ ከጎህ ቤቶች ባንክ እንጠብቃለን ብለዋል።
አስተዳደሩ ለቀጣይ 10 አመታት በትኩረት ከያዛቸው እቅድ መካከል የቤት ፍላጎትን ማቃለል አንዱ በመሆኑ በአስተዳደሩ አቅም ተገንብቶ ለነዋሪው ከሚተላለፉ ቤቶች በተጨማሪ ጎህ የቤቶች ባንክ በአስተዳደሩ የመኖሪያ ቤት ችግርን ለመቅረፍ በሚያደርገው እንቅስቃሴዎች ሁሉ የአስተዳደሩ ድጋፍ እንደማይለያቸው ገልፀዋል።
የጎህ ቤቶች ባንክ ዋና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጌታሁን ናና
በበኩላቸው እንደተናገሩት በሀገራችን ያለው የቤት ችግር በጥናት እንደተረጋገጠው በአመት 400 ሺህ ቤቶች መገንባት እንዳለባቸው ያመላክታል ይህን ክፍተት ለመሙላት ባንኩን ከዛሬ ሦስት አመት ጀምሮ እንቅስቃሴ መጀመሩን በመጠቆም ባንኩ በአራት አማራጮች ለቤት ፈላጊዋች የብድር ምችችት እንደሚያደርግም ገልፀዋል።
ባንኩ በአስተዳደሩ የቤት ችግር ለመቅረፍ በሚያደርገው እንቅስቃሴ አስተዳደሩ ከጎናችን እንደሚሆን ሙሉ እምነቴ ነው ብለዋል።


