በሦስት ወራት ውስጥ ለሰብአዊ ድጋፎችና መልሶ ማቋቋም በአይነትና በገንዘብ 300 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሀብት ለማሰባሰብ ታቅዷል- የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
በ3 ወራት ውስጥ በሚከናወን የሰብአዊ ድጋፎችና መልሶ የማቋቋም ስራ በአይነትና በገንዘብ 300 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሀብት ለማሰባሰብ እንደታቀደ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ገለጹ፡፡ ሚኒስትሯ ዛሬ በድሬዳዋ ከተማ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የወጣት አደረጃጀቶች የሰብአዊ ድጋፎችና መልሶ የማቋቋም ስራዎችን ለመስራት ከታህሳስ 1/2014 – የካቲት 30/2014 የሚከናወነውን ሀብት ማሰባሰብ ለማሳካት…


