ለ 16 ኛው የኢትዮጲያ ብሄር ብሄረሰቦች ቀን በአል የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ ።
16 ተኛው የኢትዮጲያ ብሄር ብሄረሰቦች ቀን በአል በድሬዳዋ አስተዳደር አዘጋጅነት የፊታችን ህዳር 29 የሚከበር ሲሆን በአስተባባሪነት ደግሞ የኢትዮጲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው ። ለዚሁም በአል ይሆን ዘንድም የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን በተለይም በድሬዳዋ አስተዳደር በሚከበረው በአል ላይም ሀገር አቀፍ ሲምፖዚየም ፣ የህዳሴ ግድብ ዋንጫ ለቀጣዩ ክልል ማስረከብ ፣ ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት የደም ልገሳ…


