የድሬደዋ አስተዳደር የ2014 በጀት አመት የ4ኛው ሩብ አመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል፡፡

    የ2014 በጀት አመት የ4ኛው ሩብ አመት የማዘጋጃ ቤታዊ ፣ የሴክተር መ/ቤቶች ፤የከተማ ቀበሌዎችና የገጠር ክላስተሮች የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ መድረክ ከሰኔ 27-28 /2014 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡
    በዛሬው እለት በተጀመረው የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ መድረክ በጠዋቱ መረሀ ግብር የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ፤የትምህርት ቢሮ ፣የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ፣የኮንሰትራክሽንና ቤቶች ልማትቢሮ፣ ግብርና ውሀ ማአድንና ኢነርጂ ቢሮ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ይቀርባል፡፡