ቀፌራን አቋርጦ የሚሄደው የደቻቶ ወንዝ ሀፍካት ድልድይ ድረስ የፅዳት ስራ በዛሬው እለት ተከናውኗል።

    33 ኛው የፅዳት ዘመቻ በዛሬው እለት የአስተዳደሩ አመራሮችና ማህበረሰብ እንዲሁም ባለሀብቶችና የስራ ተቋራጮች በንብረታቸውና በጉልበታቸው የተሳተፉበት መሆኑ ለየት ያደርገዋል ያሉት የአስተዳደሩ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር ጀማል ኢብራሂም ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ቀኑ 6 ሰአት የቆየ የፅዳት ዘመቻ መሰራቱን ገልፀዋል።
    ቀደም ሲል አካባቢው ህገወጥ ድርጊት የሚሰራበት በመሆኑ በቀጣይ ማህበረሰቡ ቆሻሻ የሚያስወግድበት ቦታ በአካባቢው ያሉትን ነዋሪዋች በሴፍትኔት በማደራጀት በሚዘጋጀው ቦታ ተዘጋጅቶ ቆሻሻው እንደሚወገድና አስተዳደሩም አካባቢውን አረንጓዴ ልማት እንደሚያለማበት ኢንጅነር ጀማል ገልፀዋል።
    ኢንጅነር ጀማል ባስተላለፉት መልዕክትም በቀጣይ ሳምንት ለሚኖረው የፅዳት ዘመቻ በአስተዳደሩ የሚኖሩ ባለንብረቶች እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።