የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እና የቢሮው ተጠሪ ተቋም የሆነው ድሬዳዋ ሥራ አመራርና ካይዘን ኢንስቲትዩት አመራሮች አና ሠራተኞች የተረከቡትን የወ/ሮ አሁዶ ጅብሪል የመኖሪያ ቤት እድሳት በዛሬው እለት ጀመሩ።
በአስተዳደር ደረጃ በየአመቱ በሚከናወነው የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ለመሳተፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እና የቢሮው ተጠሪ ተቋም የሆነው ድሬዳዋ ሥራ አመራርና ካይዘን ኢንስቲትዩት አመራሮች አና ሠራተኞች የአንድ አቅመ ደካማን ቤት ለማደስ ወስነው የቤት እድሳቱን ስራ የሚያስተባብር ኮሚቴ በአስተዳደር ደረጃ በዚህ ክረምት ለእድሳት ከተመረጡ ቤቶች መካከል አንዱ የሆነውን በ01 ቀበሌ የሚገኘውን…


