የናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር በአስተዳደሩ ስር ለሚገኙ አስራ አንድ ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አደረገ
#DGC መስከረም 9 /2016 የድሬዳዋ ናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር ከአንድ ነጥብ ሁለት ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶችን በዛሬው እለት በገጠር እና በከተማ ለሚገኙ አስራ አንድ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አድርጓል፡፡ የናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ሚስተር ሊኡ ጄሽንግ በድጋፍ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ፋብሪካው አገር ከመገንባት ባሻገር የትምህርቱን ዘርፍ…


