በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል ጥቅምት 23/2015 የተካሄደው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ በተግባር የተፈፀመበትና ትምህርት የሚቀሰምበት መሆኑ ተገልጿል።
የስምምነቱን ሂደት በተመለከተና ከስምምነቱ ሌሎች ምን እንማር? በሚል በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቧል ።
ስምምነቱ በአፍሪካውያን እንዲፈፀም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከመጀመሪያው ቀን ጀምረው በቁርጠኝነት መስራታቸውም ተገልጿል ።
የሰላም ስምምነቱ ከወረቀት ባለፈ በተግባር የታየበት መሆኑም ነው የተገለፀው።
የአፈፃፀም ሪፓርቱን ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን አባል ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የፌዴራል መንግሥትን በመወከል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፌዴራል መንግሥት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት አመራሮች ተገኝተዋል።
EBC


