የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ጨምሮ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በ13ኛው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች እና 4ኛው ከ18 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ለመታደም ማምሻውን ድሬዳዋ ከተማ ገቡ

እንግዶቹ በድሬዳዋ ዓለምአቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ካሊድ መሀመድ፣ በድሬዳዋ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ዮናስ በትሩ እንዲሁም በአስተዳደሩ በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

በተጨማሪም እንግዶቹ በከተማዋ የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን እንዲሁም ሻምፒዮናው የሚካሄድበት ድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ጎብኝተዋል።

በኤደን ሳሙኤል

ፎቶ:-ቴድሮስ ልዑልሰገድ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *