በድሬዳዋ አስተዳደር የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ ዛሬ በድሬዳዋ አስተዳደር ታላቅ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው። በአሁን ሰዓት በአስተዳደሩ የሚኖሩ ነዋሪዋች ወደ እስታዲየም የተለያዩ መፈክሮችን ይዘው በመግባት ላይ ይገኛሉ ። የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የድጋፍ ሰልፉን የተመለከቱ ዘገባዎችን ተከታትሎ ባሉት የዲጂታል ሚዲያ አማራጮቹ የሚያቀርብ ይሆናል።


