የ2018 የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎች

ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በ6ኛው የሁለቱ ምክር ቤቶ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር የ2018 የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎችን በዝርዝር አስቀምጠዋል። እነዚህም፦ አድኛ፥ ከሥርዓት መለዋወጥ ጋር የማይናዱ ነፃ፣ ገለልተኛ እና ሕዝባዊ ብሔራዊ ተቋማት ለመፍጠር መንግሥት ፅኑ መሠረት በመጣል ላይ ይገኛል ብለዋል። በተያዘው የበጀት ዓመትም አንድነታችንን እና ሰላማችንን በማይናወጥ ደረጃ ላይ ለማድረስ መንግሥት በተቋማት ግንባታ…

Read More

ቀጣዩ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ተአማኒ እንዲሆን ይሠራል – ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀሥላሴ

በቀጣይ ዓመት የሚካሄደው ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና በኢትዮጵያውያን ዘንድ ተአማኒ እንዲሆን መንግሥት በኃላፊነት እንደሚሠራ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀሥላሴ ተናገሩ። ፕሬዚዳንቱ ለሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፤ የመንግሥት ትኩረት አቅጣጫዎች ከሆኑት ጉዳዮች መካከል ቀጣዩን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ ማድረግ እንደሆነ ጠቁመዋል። “መላው የሀገራችን ሕዝብ ኢትዮጵያ ያቀደቻቸውን እና የጀመረቻቸውን…

Read More

በ2017 በጀት ዓመት 8.8 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ ተችሏል – ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ

ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት 8.8 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን ገለጹ። መንግሥት ኢኮኖሚውን ከዕዳ ጥገኝነት በማላቀቅ፤ በራስ አቅም ችግሮችን በመፍታት እና ወደ ራስ ቻይ አምራችነት ለማሸጋገር ባደረገው ጥረት፤ በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የሀገሪቷ ኢኮኖሚ 8.8 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡንም ነው ያነሱት። ፕሬዚዳንቱ መንግሥት የልማት አቅጣጫዎቻችን ውስን ከሆኑ ዘርፎች ወደ ተለያዩ እና በርካታ ዘርፎች…

Read More

ይህ ዘመን በታሪካችን ውስጥ በጉልህ የሚነሳ ነው፡- ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ

ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ይህ ዘመን በታሪካችን ውስጥ በጉልህ የሚነሳ ነው ሲሉ ገልጸዋል። እኛ ኢትዮጵያውያን ለበርካታ ዘመናት ስንቆጭባቸው የነበሩትን ታላላቅ ፕሮጀክቶች ያስመረቅንበት ልዩ ዓመት አሳልፈናል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ የትውልዱ ቁጭት የነበረውን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አጠናቀን ታሪክ ሰርተናል ብለዋል። በመስከረም ወር…

Read More

የዲፕሎማሲያችን ማጠንጠኛው ብሔራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ነው፦ ፕሬዚዳንት ታየ አፅቀ ሥላሴ

ፕሬዚዳንት ታየ አፅቀ ሥላሴ በሁለቱ ምክር ቤቶች የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የዲፕሎማሲያችን መሰረታዊ ማዕከል እና ማጠንጠኛው ብሔራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በመደርጀት ላይ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህ ስትራቴጂያዊ ምርጫ ከታዛቢነት ወደ አጀንዳ ተላሚነት እና ተጽዕኖ ፈጣሪነት ለመሸጋገር አስችሎናል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪ ሀብቶቿ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ስትቀበል፤ በዛው…

Read More

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ በሁለቱ ም/ቤቶች መክፈቻ ሥነ ሥረዓት ላይ ማቅረብ ጀምረዋል

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የፌደራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ማቅረብ ጀምረዋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የሁለቱ ምክር ቤቶች አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች፣ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

Read More

የሁለቱ ምክር ቤቶች የሥራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ሥነ – ሥርዓት ተጀመረ

6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ሥነ – ሥርዓት ተጀምሯል። የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተዋል።

Read More

የኢቲቪ ፓርላማ ቻናል ተመረቀ

የኢቲቪ ፓርላማ ቻናል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በይፋ ተመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሎሚ በዶ፣ በምክር ቤቱ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቢኒያም ኤሮን ጨምሮ ሌሎች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ…

Read More