የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የሴክተር፣ የከተማ እና የገጠር ወረዳዎች ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሂዷል።
በግምገማ መድረኩ የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ይሱፍ በወቅቱ እንደገለጽት ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት እንደ ሀገር ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ አባሉን፣አመራሩንና ደጋፊውን አቀናጅቶ በማስተባበር በርካታ ስኬታማ አፈጻጽሞችን ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።
የአስተሳሰብ፣ የአመለካከትና የተግባር አንድነትና ዝግጁነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በማጠናከር የፓርቲ ኢኒሼቲቦችን በላቀ ብቃትና ቅንጅት መተግበር ያስፈልጋልም ብለዋል።
የፓርቲና የመንግስት ተልዕኮዎችን በውጤታማነት ለማሳካት ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነነት መስራት እንደሚገባ አንስተው በተግባር አፈጻጸም የታዩ ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ በማስቀጠል ክፍተቶችኝ ነቅሶ በመለየት ለቀጣይ ስኬታማ አፈጻጸም መትጋት ይጠበቃል ብለዋል።
በግምገማ መድረኩም በብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ጽ ቤት ኃላፊ ልዩ አማካሪ አቶ ዮናስ ጥግነህ የ2018 ዓ.ም በጀት አመት በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ ተግባራት ያቀረቡ ሲሆን የብልፅግና ህብረቶችን ማጠናከር፣ወጣቶችን ከማብቃትና ከማጠናከር አንፃር ፣ የአስተዳደሩን ነባራዊ የፖለቲካ ሁኔታ መረጃዎችን በወቅቱ በመሰብሰብና ማደረጃት ፣ በሁሉም መስክ የህዝብ ተሳትፎን እና ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ማጎልበት ፣ከማዕከል የወረድ የፖለቲካ እሳቤ ስርዓትን ከማስረጽ አንጻር የተሰሩ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን በሪፖርቱ አብራርተዋል።
በተጨማሪም የብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።


