የድሬዳዋ አስተዳደር በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገለፀ

******************

የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ በአመራር ዘመናቸው ለሙስሊሙ ማኅበረሰብ አንድነት እንዲጠናከር እና ተቋሙ በሕግ ዕውቅና አግኝቶ እንዲቋቋም ባደረጉት በጎ አስተዋጽኦ ይታወሳሉ ።

ለሀገራችን ሰላምና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት መጎልበት በቅንነት ያደረጉት አስተዋፅዖ ሁሌም የሚዘከር ነው ።

አስተዳደሩ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሃይማኖቱ ተከታዮችና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን ተመኝቷል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *