የሐዘን መግለጫ

የድሬዳዋ ደወሌ የምድር ባቡር ድርጅት ቦርድ አባላት በድሬዳዋ ደወሌ የምድር ባቡር ድርጅት ባቡር ላይ በደረሰ አደጋ ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማቸው ገለፁ

አባላቱ ሀዘኑ የመላው ኢትዮጲያውያን መሆኑን ገልፀው፤ ቦርዱ ከተጎጂዎች ጎን በመቆም አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ እና ይህም በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።

የቦርዱ አባላት በአደጋው ሳቢያ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች ለቤተሰባቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን የተመኙ ሲሆን፤ ቀላል እና ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተጎጂዎችም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገግሙ ርብርብ እንደሚደረግ ገልፀዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *