ልዑኩ ድሬዳዋ ከተማ የገባው በድሬዳዋ እየተገነባ የሚገኘውን የመስራቅ ኢትዮጵያ ፈጥኖ ደራሽ ካንብ ግንባታን ለመጎብኘት እንዲሁም የሀረር ፖሊስ ሆስፒታል ማስፋፊያ ግንባታ ፕሮጀክትን የስራ ሂደት ለመመልከት መሆኑ ተገልጿል።
ልኡኩ ድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር አለሙ መግራ እንዲሁም በአስተዳደሩ በሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።


