ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት ዝናሽ ታያቸው የከተማዋን የኮሪደር ልማትና የከተማ እድሳት ጉዞ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን ዛሬ በይፋ መርቀው ከፍተዋል።

‎በ5.7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ሁሉን አቀፍ ፕሮጀክት፤ የኦሎምፒክ ደረጃን ያሟላ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስ፣ የእጅ ኳስ እና የሜዳ ቴኒስ ሜዳዎችን እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን፣ ዘመናዊ የቤት እና የዉጪ ጂም ጨምሮ በርካታ ዘመናዊ የስፖርት መሰረተ ልማቶችን ከማህበረሰብ አገልግሎቶች ጋር አቀናጅቶ የያዘ ነው። ልማቱ ሁሉንም የእድሜ ክልሎች ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፣…

Read More

‎”ታላቋን ኢትዮጵያ ማለም ብቻ ሳይሆን በተግባር እንገነባታለን!” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ታላቋን ኢትዮጵያ ማለም ብቻ ሳይሆን በተግባር እንገነባታለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የከተማችንን እድሳት ለማፋጠን እና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፌስቡክ የማኅበራዊ ትስስር መተግበሪያ ባጋሩት መልዕክት። በ5.7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል ዛሬ መርቀን ከፍተናል። ‎በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው። ‎ የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን፣ እንዲሁም…

Read More

አርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ውስጥ የተገነባው አዲሱ ዘመናዊ የምርምር ሕንፃ እና ፋይዳዎቹ:-

– 34 ዘመናዊ ላቦራቶሪዎች – የላቁ የጄኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) መሠረተ ልማቶች፣ – የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን አካቷል። ‎ ተቋሙ ለሥልጠና እና ለምርምር የተመደቡ ቦታዎችን የያዘ ሲሆን በኢትዮጵያ እና በመላው አፍሪካ ለሳይንስ ሥነ ምሕዳር መስፋፋትና አቅም ግንባታ አዲስ መለኪያ አስቀምጧል።

Read More

“ኢትዮጵያ ክትባት ማምረት አትችልም” የሚለውን ምልከታ የቀየረው የምርምር ማዕከል

ኢትዮጵያ በመድኃኒትና በክትባት ምርት ራሷን ለመቻል የምታደርገውን ጥረት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ግዙፍ የምርምር ማዕከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ተመርቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ማዕከሉን በመረቁበት ወቅት፥ ከዚህ ቀደም ይህን መሰል መሰረተ ልማት ባለመኖሩ “ኢትዮጵያ መድኃኒትና ክትባት ማምረት አትችልም” በሚል የምናቀርበውን የአጋርነት ጥያቄ ብዙዎች ሳይቀበሉት ቀርተዋል ብለዋል። የዚህ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መገንባት ያንን…

Read More

“በአምስት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን መድኃኒት ሙሉ በሙሉ በራሷ አቅም ታመርታለች” – ጠቅላይ ሚነስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)::

በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን መድኃኒት ሙሉ በሙሉ በራሷ አቅም እንደምታመርት ጠቅላይ ሚነስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባውን ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀው በከፈቱበት ወቅት ኢትዮጵያ በመድኃኒት ምርት ራስን ለመቻል የሄደችበትን ርቀት አብራርተዋል። በአንድ ሀገር ውስጥ ችግር እና ተግዳሮቶች ሲፈጠሩ ከመሸበር ይልቅ ችግሩን እንደ ዕድል መጠቀም እንደሚያስፈልግ…

Read More