የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ለ85ኛው የአርበኞች ድል መታሰቢያ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ያስተላለፉት መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል መላው የድሬዳዋ አስተዳደር ነዋሪዎችና የሀገራችን ሕዝቦች፤ እንኳን ለ85ኛው የአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! ይህ ታላቅ የድል በዓል አባቶቻችንና እናቶቻችን፣ እንዲሁም በየዘመናቱ የነበሩ ወጣቶቻችንና እህቶቻችን ለታላቋ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ለጥቁር ሕዝቦች ነፃነት የከፈሉትን ወደር የሌለው መስዋዕትነት የምንዘክርበት ታሪካዊ ዕለት ነው። አርበኞቻችን ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን ትተው በጋራ በመቆማቸው ሀገርን ከወራሪ ማዳን…


