ብልፅግና ፓርቲ በጅግጅጋ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በስኬት አጠናቋል።
የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊ የምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ፣ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዲሁም የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች በተገኙበት በዚህ መድረክ ላይ የሚከተሉት አበይት ጉዳዮች ተገምግመዋል::
ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዕቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫ እና በምርጫው ወቅት የነበሩትን ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞች በዝርዝር ለይቷል።
በድህረ ምርጫ ወቅት ትኩረት በሚሹ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት በመደረግ የቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ለተሳታፊ አመራሮቹ፣ ለክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ለከንቲባዎቹ የሶማሌን ሕዝብ ወግና ባህል የሚያንጸባርቁ የባህላዊ አልባሳትና የተለያዩ ማስታወሻ ስጦታዎችን አበርክተዋል።


