የከተራ በዓል እየተከበረ ነው

    የከተራ በዓል በድሬደዋ አስተዳደር ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል።
    ታቦታት ከአድባራት ወጥተው በካህናት፣ በዲያቆናት እና በምዕመናን ታጅበው ወደ ጥምቀተ ባህሩ በመጓዝ ላይ ይገኛሉ።
    የጥምቀት በዓል በየአመቱ በሀገራችን የክርስትና እምነት ተከታዮች በአደባባይ ከሚከበሩ ሀይማኖታዊ በዓላት አንዱ ነው።