በድሬዳዋ አስተዳደር የቀበሌ 02 ብልጽግና ፓርቲ ለተወካዮች፣ ለከተማና ለቀበሌ ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪዎች በማቅረብ ከህብረተሰቡ ጋር የማስተቸትና የውይይት መድረክ አካሄደ።

    የማስተቸትና የውይይት መድረክ የተካሄደው በሁለት መሰብሰቢያ አዳራሽ የቀበሌውን ነዋሪዎች በመክፈል ሲሆን አስተዳደሩን ወክለው በእጩነት የቀረቡ 2 የተወካዮች ም/ቤት እጩዎች፣ 9 ለከተማና 300 ለቀበሌው ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪዎች ቀርበው ህብረተሰቡን የማስተቸት ስራ ተከናውኗል። መድረኩ በቀበሌው ድጋፍ ሰጪ አመራሮችና የፓርቲው አስተባባሪዎች ተካሂዷል። በትላንትናው እለት ተመሳሳይ መድረኮች በ8 ከተማ ቀበሌዎችና በ4 ገጠር ክላስተሮች ተከናውኗል። ምንጭ፦# DD #PP

    Read More

      ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን # እንደርሳለን!” 5ተኛዉ ሀገር አቀፍ # የእግረኞችና # የብስክሌተኞች ቀን በተለያዩ በድሬደዋ በተለያዩ መርሀግብሮች በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

      በድሬደዋ ከተማ በተካሄደዉ መድረክ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያስተላለፉት በፌደራልትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬደዋ ቅርንጫፍ ጽ/ት ኃላፊ ወሮ ሰአዳ አዋሌ እንደተናገሩት የሞተር አልባ ትራንስፖርትና የእግር ጉዞን ማህበረሰቡ እንደባህል እንዲጠቀም ለማበረታታት በየወሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው መርሀግብር እንደ ድሬደዋ በማህበረሰቡን በመነቃቃት ለውጥ እያመጣ እንዳለ ጠቁመዋል፡፡ በዚሁ በትራንስፖርት ሚኒስትርና ትራንስፖርት ባለስልጣን ድሬደዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትበቅንጅት በሚዘጋጀው መርሀግብር በየወሩ የሳታፊ ቁጥር…

      Read More

        የድሬዳዋ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት በአስተዳደሩ ከሚገኙ ባለሀብቶች ጋር የምክክርና ሀብት የማሰባሰብ መድረክ አካሄደ::

        ሀገር ከድህነት ቀንበር እንድትወጣና ልማቷ በአስተማማኝ ደረጃ ላይ ደርሶ የዜጎች ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ከመንግስት ቁርጠኛ አመራርና ከህዝቦች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ባሻገር የባለሀብቶች ሚና ከፍተኛ ቦታ የሚይዝ መሆኑን የአስተዳደሩ ም/ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ መድረኩን በከፈቱበት ጊዜ ተናግረዋል። የድሬዳዋ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መብራቴ ገብረየስ የፓርቲውን ጥቅል ዓላማ፣ መለያ ዕሴቶች፣ የፖለቲካ ፕሮግራም፣ የኢኮኖሚ ፕሮግራም፣ ማህበራዊ ፕሮግራም እና…

        Read More