ሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መሳሪያ በሀገር ውስጥ አቅም በማምረት ለኮቪድ 19 ፅኑ ህሙማን ለማድረስ እያደረገ ያለው ጥረት እየተሰናከለ መሆኑን ሬዳዋ ሞተርስ ኢንዱሰትሪ ኃ/የተ/የግ ማህበር አስታወቀ፡፡
መቀመጫውን ድሬዳዋ ያደረገው ሬዳዋ ሞተርስ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የኢንጅነሪንግ ክፍል ማናጀር ኢንጅነር ምንያህል ደበበ እንደተናገሩት ድርጅቱ በአሁን ሰአት የበርካቶችን ህይወት እየቀጠፈ የሚገኘውን የኮቪድ 19 ወረርሽን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ፡፡ ድርጅቱ ወርሽኙ ከተከሰተ ወዲህ ከፍተኛ እጥረት የሚታይበትን ሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መሳሪያ (መካኒካል ቬንትለት) በሀገር ወስጥ በራስ አቅም ለማምረት ሰፊ ግዜና በጀት…


