የተፈጠረውን የኦክስጂን እጥረት ለማቃለል ባለሀብቶች ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል ተባለ፡፡

    በድሬዳዋ ጤና ቢሮ የኮቪድ-19 ህክምና ማዕከል ለሆነው የፈረንሳይ ሆስፒታል ክሮምቶ ማኑፋክቸሪንግ ፒልሲ 50 ኦክስጂን የተሞላባቸውን ሲሊንደሮች በድጋፍ አበርክቷል፡፡ በድጋፍ አሰጣጡ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ዕለት ተዕለት የኮቪድ-19 ስርጭት መጠን መስፋፋቱን ተከትሎ በአስተዳደራችን የህሙማን ቁጥርም በመጨመሩ ምክኒያት የተከሰተውን የኦክስጂን እጥረት ግምት ውስጥ በማስገባት ክሮምቶ ማኑፋክቸሪንግ ፒልሲ ላደረገው የኦክሲጂን ሲሊንደሮች ድጋፍ ምስጋናቸውን…

    Read More

      ስፖርታዊ ውድድሮች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውን በማሻሻል የሀገር ልማት ላይ ከፍተኛ ፋይዳ እንዲኖረው ከማድረግ በዘለለ ለወጣቶችም የስራ እድል እንዲፈጥር መሰራት እንዳለበት ተገለፀ፡፡

      በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ ለሚገኘው የቤትኪንግ ኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር መሳካት የጎላ ሚና ለነበራቸው አካላት የእውቅና ፕሮግራም ተዘጋጅቷል፡፡ የ 2013 የቤትኪንግ የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ ይገኛል፡፡ 4 ተኛው ዙር የቤትኪንግ የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ 13 ክለቦች ተሳታፊ ሆነው ውድድራቸውን እያካሄዱ ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞም ውድድሩ በተሳካ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱ የሚዲያ…

      Read More

        የድሬዳዋ ልጆች እና ወዳጆች አለም አቀፍ ማህበር” ለአቅመ ደካማ ነዋሪዎች ድጋፍ አደረገ::

        በአስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን ሁለገብ ሜዳ በተካሄደው የድጋፍ መርሀግብር ላይ ወ/ሮ ሜላት ብርሀኔ ማህበሩን በመወከል ባደረጉት ንግግር በአሜሪካና በአውሮፓ በሚኖሩ የድሬዳዋ ተወላጆች የተመሰረተው ማህበር በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ሰብአዊ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል:: በዛሬው ድጋፍም ከተለያዩ የአስተዳደሩ የከተማ ቀበሌዎች ለተመረጡ 200 አቅመ ደካማ የእስልምና እና ክርስትና እምነት ተከታዮች በዓል መዋያ የሚሆን ለእያንዳንዳቸው 1ሺህ ብር…

        Read More