በሐረሪ ብሄረሰብ ዘንድ በድምቀት የሚከበረውን የሸዋል ኢድ በዓል በዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
1442ኛው የሸዋል ኢድ በዓል በድሬደዋ የሐረሪ ብሄረሰብ ተወላጆች በዛሬው እለት በድሬደዋ ሚሊኒየም ፓርክ በድምቀት ተከብሯል፡፡ ከታላቁ የረመዳን ፆም ፍቺ አምስት ቀናት በኋላ ተከብሮ የሚውለው ሸዋል ኢድ በሐረሪ ብሄረሰብ ዘንድ በድምቀት እንደሚከበር የገለጹት በድሬደዋ የሃረሪ ኮሚዩኒቲ አስተባባሪ አቶ ዜዳን በክሪ በዓሉ በብሄረሰቡ ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው ብለዋል፡፡በዓሉን በዩኔስኮ የማይዳሰሱ ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ነው…


